የታለቁ ጉዞ ወደ ሀገር ቤት መርሃ ግብር ይፋ ሆነ

የታለቁ ጉዞ ወደ ሀገር ቤት መርሃ ግብር ይፋ ሆነ

በታላቁ ጉዞ ወደ ሀገር ቤት ጥሪ መሰረት ወደ ሀገር ቤት የሚመጡ ዳያስፖራዎች በሚኖራቸው ቆይታ የሚሳተፉባቸውን መርሃ ግብሮች ብሄራዊ አስተባባሪ ኮሚቴው ዛሬ ይፋ አድርጓል።

የብሄራዊ ኮሚቴው የኦፕሬሽናል ዘርፍ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አምባሳደር ብርቱካን አያኖ እንግዶችን ተቀብሎ ለማስተናገድ የተቀናጀ ዝግጅት መደረጉን አንስተው፣ ዳያስፖራው ሀገር ችግር በገጠማት ጊዜ በሚችለው ነገር ሁሉ አኩሪ ተግባር ሲያከናውን እንደነበር አስታውሰዋል። ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም የአሁን ጥሪ ዳያስፖራው ሀገሩንና ወገኑን በዘላቂነት እንዲያግዝ መሰረት የሚጣልበት መሆኑን ጠቅሰዋል።

ጥሪውንና ዳያስፖራው የመጣበትን አላማ ማሳካት የሚያስችሉ መርሃግብሮችም መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል።የብሔራዊ ኮሚቴው ሴክሬታሪያትና የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሐመድ እንድሪስም ከታለቁ ጉዞ ወደ ሀገር ቤት ጥሪ ጋር በተያያዘ በብሔራዊ ኮሚቴው የጸደቀውን የሁነት መርሃ ግብር አቅርበዋል። በዚህም መሰረት ታህሳስ 20፣2014 ዓ/ም በወዳጅነት ፓርክ ይፋዊ የእንኳን ደህና መጣችሁ ፕሮግራም እንደሚኖር ገልጸዋል። የ

መክፈቻ ስነ ስርዓቱን ተከትሎም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና በክልሎች የሚከናወኑ ሁነቶችን በዝርዝር አቅርበዋል (የሁነቶቹን ዝርዝር ከዚህ ዜና በኋላ ራሱን አስችለን የምናቀርብ መሆናችንን እንገልጻለን)።የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታዋ ክብርት ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊትም በበኩላቸው ዳያስፖራው በቱሪስት መዳረሻ ቦታዎች ላይ በአግልግሎት አሰጣጥ ላይ ያልተፈለገ ችግር እንዳይገጥመው በቂ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመዋል።

ይህንን አስምልክቶም ከክልሎችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተገቢ ውይይት መደረጉን ጠቁመዋል።የብሄራዊ ኮሚቴው አባል የሆነውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን በመወከል የተገኙት የከተማ አስተዳደሩ ም/ከንቲባ ክቡር አቶ ዣንጥራር ዓባይም ዳያስፖራው በቆይታው ያለ ምንም እንግልት የሚፈልጋቸውን አገልግሎቶች እንዲያገኝ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን ጠቁመዋል። ከተማው ውስጥ የሚደረጉ ኩነቶችም ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከናወኑ ለማድረግ የተቀናጀ የቅድመ ዝግጅት ስራ መከናወኑንም ጠቅሰዋል።

Facebook
Twitter
Telegram
WhatsApp

Related Content

Frequently Asked Questions (FAQ)s

People having an Ethiopian Origin ID, whether active or expired, are not required to obtain a visa to enter Ethiopia. Others should apply for a visa online or apply for a visa on arrival.

Passengers must present a medical certificate showing a negative COVID-19 test result before boarding a flight to Ethiopia. The test should be taken at most 120 hours before arrival.

People with Ethiopian Origin ID either active or expired can enter to Ethiopia with out visa. But they need to show either the active or the expired Ethiopian Origin ID at the airport counters. 

Ethiopian that hold non-Ethiopian passport can apply for Ethiopian origin ID online. It will be processed within 15 Days.

Please visit https://www.moh.gov.et/site/Donation_For_Health_Facility_Restoration for Steps and Procedures to Facilitate Donations of Medicines, Medical Supplies and Equipment For Health Facility Restoration.

Please visit respective hotels website to book your hotels

Please check our website for the list of tour operators that offer discount of up to 30%.

Get in touch with us

We are here to help!