Great Ethiopian Homecoming Welcoming Program

ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ እንግዶችን ለመቀበል የተቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ ዝግጅቱን አጠናቀቀ

ታህሳስ 13 ቀን 2014 (ቱሚ) መንግስት አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆችን ለመቀበል የሚያደርገውን ዝግጅት ማጠናቀቁን ገለጸ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በውጭ አገር የሚኖሩ አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እስከ ታህሳስ 29 ቀን 2014 ዓ.ም ወደ አገር ቤት እንዲመጡ ጥሪ ማድረጋቸው ይታወቃል።
የአገር ቤት ጥሪውን የሚያስተባባር ብሔራዊ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ስራ መግባቱ የሚታወቅ ሲሆን፤ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የሚመራው ኮሚቴ በዝግጅቱ ዙሪያ ዛሬ ውይይት አድርጓል።
ኮሚቴው ዳያስፖራው ወደ አገር ቤት በሚመጣበት ወቅት ከቪዛ አሰጣጥ፣ ትራንስፖርት፣ የእንግዶች ማረፊያና ሌሎች አገልግሎት መስጫዎች ጋር በተያያዘ ምቹ መስተንግዶ እንዲያገኝ ከማድረግ አኳያ እየተከናወኑ ባሉ ስራዎች ላይ መምከሩን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።

ወደ አገር ቤት የሚመጡ ዳያስፖራዎች በአገር መልሶ ግንባታ ሂደትና የውጭ ሃይሎችን ያልተጋባ ጫና በመቃወም በሚካሄዱ ሰላማዊ ሰልፎች ላይ የሚሳተፉባቸው የተለያዩ መርሃ ግብሮች መዘጋጀታቸውን አመልክቷል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የመንግስትና የግል ሆቴሎችና ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ አገር ቤት ለሚመጡ ዳያስፖራዎች የዋጋ ቅናሽ እንደሚያደርጉ ማሳወቃቸው ተወስቷል።

Facebook
Twitter
Telegram
WhatsApp

Related Content

Frequently Asked Questions (FAQ)s

People having an Ethiopian Origin ID, whether active or expired, are not required to obtain a visa to enter Ethiopia. Others should apply for a visa online or apply for a visa on arrival.

Passengers must present a medical certificate showing a negative COVID-19 test result before boarding a flight to Ethiopia. The test should be taken at most 120 hours before arrival.

People with Ethiopian Origin ID either active or expired can enter to Ethiopia with out visa. But they need to show either the active or the expired Ethiopian Origin ID at the airport counters. 

Ethiopian that hold non-Ethiopian passport can apply for Ethiopian origin ID online. It will be processed within 15 Days.

Please visit https://www.moh.gov.et/site/Donation_For_Health_Facility_Restoration for Steps and Procedures to Facilitate Donations of Medicines, Medical Supplies and Equipment For Health Facility Restoration.

Please visit respective hotels website to book your hotels

Please check our website for the list of tour operators that offer discount of up to 30%.

Get in touch with us

We are here to help!